Tuesday, June 17, 2014

አዜብ መልቀቂያ አስገቡ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

አዎ እኔም የእብድ የቃውስ የሸርሙጣ ትርጉም ለነፃነት የሚታገሉ ኢትዮጵያዊነትን የሚሰብክ ግፈኞችን የሚታገል…ለኢትዮጵያዊነት የሚኖር ከሆነ አዎ እብድ ነኝ አዎ ቀውስ ነኝ አዎ ሸርሙጣ ነኝ እላቸዋለው፡፡
አዜብ መልቀቂያ አስገቡ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)
ወ/ሮ አዜብ መስፍን ለሕወሐት ማ/ኮሚቴ የመልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ምንጮች አስታወቁ። ከባለቤታቸው ህልፈት በኋላ በፓርቲው የነበራቸው ተሰሚነትና የበላይነት እየተሸረሸረ በመምጣቱና ከኤፈርት ሃላፊነታቸው በመነሳታቸው እንዲሁም ጓጉተውለት የነበረው የአዲስ አበባ ከንቲባነት ስልጣን በማጣታቸው፣ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ በመግባታቸው ምክንያት ለፓርቲው የመልቀቂያ ጥያቄ ማቅረባቸውን ምንጮቹ አስረድተዋል። በተጨማሪ አዜብ ይተማመኑባቸው የነበሩት ሹማምንት ከስልጣን እየተገፉ ገሚሶቹም እስር ቤት መወርወራቸው እንዲሁም በስብሃት ነጋ ቡድን እየተወሰደባቸው ያለው ፖለቲካዊ የበላይነት መቋቋም ስለተሳናቸው ከፓርቲው በግዜው መሰናበት እንደመረጡ ከምንጮቹ መረዳት ተችሏል። አዜብ መስፍን ላቀረቡት የመልቀቂያ ጥያቄ ፓርቲው በቅርቡ ምላሽ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ያመለከቱት ምንጮች፣ አያይዘውም ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ አዜብ በሲውዲን ወይም አሜሪካ ቨርጂኒያ በገዙት መኖሪያ ቤት ጠቅልለው ሊገቡ እንደሚችሉ አመልክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ከኢታማጆር ሹመታቸው በማስነሳት በምትካቸው በቅርቡ ሌ/ጄ ተደርገው የተሾሙትን ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀልን ለመተካት መታቀዱን ምንጮች ጠቁመዋል።
Let me comment on this
እዚህ ጽሑፍ ውስጥ ያልተካተቱ እውነቶች
1) የጀነራል ሳሞራ የኑስ ጤንነት አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ስለደረሰ በስምምነት የተደረገ ውሳኔ ስለመሆኑ
2) አዜብ በህውሃት የመተካካት ልምድ ሳይሆን ቀድሞ የታቀደ ነገር ነው እየሆነ ያለው ። አሁን ማን ይሙት አዜብ ስልጣን ይዛ መሪ ምናምን ሆና መኖር ትፈልግ ነብር ማለት ነውን ( ከመልስ ሞት በሁዋላ ?) ለማያውቅሽ ታጠኝ ዜና ነው ! አይደለም አሁን እሱዋ የህውሃት ጡረተኛ ነች ። አፍ ይለጎማል ሆድ ይደጎማል !
3) አቦይ ስብሃትን ያገኘናቸው ህውሃት ወይስ እንግሊዝ ? ውስጡን ለቄስ ወይስ ውስጡን በመቀስ እንዳይንቀሳቀስ ። ማን ነበረ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች በሚል እህል አስመስሎ መሳሪያ ለመቀበል ከ ውጭ ሀገር መንግስት ጋ ተስማምቶ ያንን ስምምነቱን እውን ያረገው ? እኔ እንጃ ። ገብርዬ ( ገብረ መድህን አርአያ ( አምድ ለናቱ )) እሱ ይንገረን እውንቱን !
ሄኖክ የሺጥላ

No comments:

Post a Comment