Tuesday, June 17, 2014

የተፈናቃዮቹ የክስ መዝገብ ዛሬ ተሰማ

አዎ እኔም የእብድ የቃውስ የሸርሙጣ ትርጉም ለነፃነት የሚታገሉ ኢትዮጵያዊነትን የሚሰብክ ግፈኞችን የሚታገል…ለኢትዮጵያዊነት የሚኖር ከሆነ አዎ እብድ ነኝ አዎ ቀውስ ነኝ አዎ ሸርሙጣ ነኝ እላቸዋለው፡፡

የተፈናቃዮቹ የክስ መዝገብ ዛሬ ተሰማ
ባለፈው ዓመት ለዓመታት ከኖሩበትና ሀብት ንብረት ካፈሩበት መኖሪያቸው እንደተፈናቀሉ በመግለጽ ይህን ተግባር ፈጽመዋል፣ አስፈጽመዋል ባሏቸው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴርና በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ቡለል ወረዳ ላይ ተፈናቃዮቹ በተወካዮቻቸው በኩል ክስ መስርተዋል፡፡
በዚህ መሰረት ዛሬ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ 8ኛ ፍትሃ ብሄር ምድብ በዋለው ችሎት የክስ መዝገቡ ተሰምቷል፡፡ ተፈናቃዮቹ በጠበቃቸው በዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም አማካኝነት እየተመሩ ክሱን እንዲያስኬዱላቸው ቄስ መስፍን አስፋውንና አቶ አቻምየለው ደሴን ወክለው አቤቱታቸውን ለፍርድ ቤቱ አሰምተዋል፡፡
ከሳሾቹ ከ15-20 ዓመታት ከኖሩበት ስፍራ ቤት ንብረታቸውን ጥለው እንዲፈናቀሉ መደረጋቸውንና ይህም ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ ወንጀል እንደተፈጸመባቸው አስረድተዋል፡፡ ክሱ የቀረበባቸው የፌደራል ጉዳዮችና የቡለል ወረዳም መልስ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከሳሾቹ ይኖሩበት በነበረው ቦታ ቤት ንብረት አላፈሩም፤ ሰዎቹ ለፖለቲካ ትርፍ ማስገኛ መጠቀሚያ እየሆኑ ነው ሲል ለችሎቱ አስረድቷል፡፡
የቡለል ወረዳ በበኩሉ ከሳሾቹ በወንጀል የሚፈለጉ እንደሆኑ ጠቅሷል፡፡ ችሎቹ ግራ ቀኙን አዳምጦ ሶስቱም አካላት ለክርክር ቀጠሮ ሰኔ 30 ድጋሜ ችሎት ፊት እንዲቀርቡ ወስኗል፡፡
ይህን የፍርድ ሂደት ለማስጀመር ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ ባካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የዜጎችን ከአመታት ከኖሩበት ቀየ መፈናቀል በማውገዝ ጉዳዩን ወደ ህግ ለማቅረብ ቃል በገባው መሰረት የተፈናቃዮችን ሁኔታ ቦታው ድረስ በመሄድና በመከታተል ለአሁኑ የህግ ሂደት እንዲደርስ ማስቻሉን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡ አሁንም ፓርቲው አጠቃላይ የፍረድ ሂደቱን በቅርበት እንደሚከታተል አቶ ዮናታን ጨምረው አስረድተዋል፡፡

No comments:

Post a Comment