Sunday, June 29, 2014

ሁሉም ያው ናቸው

አዎ እኔም የእብድ የቃውስ የሸርሙጣ ትርጉም ለነፃነት የሚታገሉ ኢትዮጵያዊነትን የሚሰብክ ግፈኞችን የሚታገል…ለኢትዮጵያዊነት የሚኖር ከሆነ አዎ እብድ ነኝ አዎ ቀውስ ነኝ አዎ ሸርሙጣ ነኝ እላቸዋለው፡፡

ሁሉም ያው ናቸው
<<በፖሊስ 28 ቀን ተጨማሪ ቀጠሮ ተጠይቆ 14 ቀን ብቻ ተፈቀደ፤ ዻኛዋ አቃቤ ህግን አስጠነቀቁ…” ምናምን የሚለው ነገር ብዙውን ጊዜ ድራማ ነው። ፍትሐዊ ዻኝነት እንዳለ ለማስመሰል የሚደረግ የተቀናጀ ጨዋታ ነው። ለህሊናውና ለሙያው ያደረ እውነተኛ ዳኛ ቢኖርማ ብርቱካን ሚዴቅሳ- ስዬን እንዳሰናበተቻችው ፦<<እኚህን ልጆች ዋስትና የሚያስከለክል ቀርቶ አንድም ቀን እስር ቤት የሚያሳድር ክስ አላገኘሁባቸውም” ብሎ ቢያንስ በዋስ ያሰናብታቸው ነበር። ይህን ስል አንዳንድ ደፋር ወሳኔ የሚሰጡ፣ለሙያቸው እና ለህሊናቸው ያደሩ ዳኞች የሉም እያልኩ አይደለም። ለምሳሌ የጦማርያኑ ክስ እንደተጀመረ ጉዳዩን ይዘውት የነበሩትንና በጦማርያኑ ላይ የተመሰረተውን የሽብርተኝነት ክስ ያልተቀበሉትን ዳኛ መጥቀስ ይቻላል። ሆኖም አልፎ አልፎ እንደዛ ያሉ ደፋር ዳኞች ብቅ ሲሉ ከሚያስችሉት ችሎት ተነስተው በሌሎች እንዲተኩ ይደረጋሉ። ብዙዎቹ ግን <<አስፈቅደው>>ለማስመሰል ደፈር ያለ ነገር እየተናገሩ በ አጉል ተስፋ ንጹሀንን የሚያሹ፣የሚቀጡና በፍትህ ስም እኩይ ተልእኮ የሚፈጽሙ ሆዳሞች ናቸው።
አንዳንዴማ ልክ ቁጪ በሉዎች ሊሰርቁ ሲሉ እንደሚፈጥሩት የውሸት አምባጉዋሮ፤ ዳኞችና አቃቤ ህጎች እርስበርስ የውሸት እሰጥ እገባ በመግባት ድራማ እስከመሥራት ይደርሳሉ።ያኔ ልጁ፣እናቱ፣አባቱ፣ወዳጁ… የታሰረበት ፍትሕ የተጠማ ወገን ከጭንቀቱ ማየል የተነሳ የሰማው እሰጥ እገባ እውነት እየመሰለው <<ዳኛው እንዲህ አሉ፣ አቃቤ ህግን ገሰጹ፣ማረሚያ ቤትን አስጠነቀቁ …ፖሊስ ይህን ያህል ቀን ተጨማሪ ቀጠሮ ጠይቆ ይህን ያህል ብቻ ፈቀዱ..” እያለ ትንሽ ተስፋ ያደርጋል።
እውነታው ግን ሌላ ነው። የችሎት ሂደቱ የሚሄድበትም ሆነ ተከሳሾች የሚቀጡበት ወሳኔ ከመጋረጃ ጀርባ በቀጭን ሽቦ የሚመጣ እንጂ ከፍርድ ቤቱ መዝገብ የሚወጣ አይደለም። አዎ፣ የፍትሕ ስርዓቱ ምንም ተስፋ የለውም-ምንም! እዛ ፍርድ ቤት የሚደረገው ነገር ሁሉ ቴአትር ነው። ጉዳዩን እያስቻሉ ያሉት ዳኞች የድርሰቱ መሪ ተዋናይ ናቸው። ለህሊናቸው ያደሩ እውነተኛ ዳኞች ንጹሀን አንድ ቀንም እንዲታሰሩ አይፈቅዱም። የእውነተኛ ዳኞች መርህ፦” አንድ ንጹህ ሰው ያለጥፋቱ ከሚታሰር፤ እልፍ ተጠርጣሪዎች ቢያመልጡ ይሻላል” የሚል ነው። እውነተኛ ዳኞች በሙያቸውና በህሊናቸው የሚመሩ እንጂ፤ በባለስልጣናት ትእዛዝ የሚሽከረከሩ አይደሉም።
እና…እኒህኞቹ ማለትም፣ 28 ቀን ቀጠሮ ሲጠየቅ- 14 ቀን እያሉ፣ ተክሳሾች በማረሚያ ቤት ተደበደብን ሲሉ ደብዳቢውን በመቅጣት ፋንታ ፦” ሁለተኛ እንዲህ ያለ ነገር እንዳይደገም…” እያሉ የሚቀልዱት ዳኞች ከዐቃቤ ህጎቹና ከባለስልጣናቱ የተለዩ አይደሉም። እንደውም ከስርአቱ ቁንጮዎችና ከዐቃቤ ህጎቹ ባልተናነሰ ሁኔታ በህግም፣በታሪክም ተጠያቂ መሆን ያለባቸው፤ ንጹሀን የሚንገላቱበትን የትእዛዝ(የድርሰት) ፍትህ በመተወን እያስፈጸሙ ያሉት እንዲህ ያሉ አስመሳይ ዳኞች ናቸው።
ድሮ ሀገሬው በጉቦ ተቸግሮ ፍትሕ ቢያጣ ጊዜ፦
የጅብ ሊቀ-መንበር፣የዝንጀሮ ዳኛ፣ የጦጣ ጸሀፊ፣
ሁሉም ሌቦች ናቸው፣ ዘራፊ ቀጣፊ>> ብሎ ነበር። አዎ፣ሁሉም ያው ናቸው።

No comments:

Post a Comment