Monday, June 30, 2014

በሑመራ በረከት አከባቢ 285 አርሶአደሮች መሬታቸው ተነጥቀው ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ተወሰነ።

በሑመራ በረከት አከባቢ 285 አርሶአደሮች መሬታቸው ተነጥቀው ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ተወሰነ። በ1997 ዓም ከደቡባዊና ምሥራቃዊ ዞኖች የተውጣጡ ሰፈርተኞች ሲሆኑ ይኸው አሁን ለዘጠኝ ዓመት ከኖሩበት አከባቢ ተፈናቅለው መሬታቸው የህወሓት ስርዓትን ለሚደግፉ ጥገኞች እንዲሰጥ ተወስኗል። አሁን መሬቱ ለካድሬዎች እየታደለ ነው። ተፈናቃዮችም አቤት የሚሉበት መድረክ አጥተዋል። መሬት የመንግስት በመሆኑ መሬት ለማግኘት ዜጋ መሆን ብቻ በቂ አይደለም። የስርዓቱ አገልጋይ መሆንም ይጠበቅብሃል። የስርዓቱ አገልጋይ ባርያ ካልሆንክ መሬት አይኖርህም። ባርያ ከሆንክ ደግሞ ምንም የለህም። It is so!!!

No comments:

Post a Comment