Thursday, June 19, 2014

አቶ ሬድዋን እዲህና እንዲያ እያሉ ነበር ቃለ መጠይቃቸውን ገፍተው አንድ እሳቸውንም ሆነ የሚውክሉትን መንግስት በእጅጉ የሚያሳንስ አስተያየት የሰነዘሩት::

አዎ እኔም የእብድ የቃውስ የሸርሙጣ ትርጉም ለነፃነት የሚታገሉ ኢትዮጵያዊነትን የሚሰብክ ግፈኞችን የሚታገል…ለኢትዮጵያዊነት የሚኖር ከሆነ አዎ እብድ ነኝ አዎ ቀውስ ነኝ አዎ ሸርሙጣ ነኝ እላቸዋለው፡፡
አቶ ሬድዋን እዲህና እንዲያ እያሉ ነበር ቃለ መጠይቃቸውን ገፍተው አንድ እሳቸውንም ሆነ የሚውክሉትን መንግስት በእጅጉ የሚያሳንስ አስተያየት የሰነዘሩት:: ሚንስትሩ “Human Rights Watch” እና “Freedom House” ከመሰሎቻቸው ጋር በመሆን በመንግስታቸው ላይ ሊሰሩት የተዘጋጁትን ክፉ ነገር እናውቃለን በሚል እንድምታ በድርጅትቹ ውስጥ ያሉት እያንዳዳቸው ግለሰቦች ማን ማን እንደሆኑና ከዚህ ቀደም ምን እና የት ይሰሩ እንደነበረ ጭምር መንግስታቸው ጠንቅቆ እንደሚውቅ ከእኛ ወዲያ ላሳር በሚል መተማመን ተናገሩ:: ለምን እንደሆነ ባላውቅም ይህን ስሰማ በአእምሮዬ ድቅን ያለብኝ ያ የቦሌው ፖሊስ የቪኦኤን ጋዜጠኛ ያለህበት መጥቼም ቢሆን አስርሃለሁ ያለው ነገር ነበረ:: ምናልባትም አቶ ሬድዋንም ፣ ያም ፓሊስም የሚናገሩትን የማያውቁና የማመዛዘንና ጉድለት ያለበት አእምሮ ተሸካሚዎች ስለሆኑ ይሆናል:: ለነገሩ ኢህአዲግ ያፈራቸው ደናቁርት ባለስልጣኑ የተናገሩትን ከጠቢብና ምሁር እንደወጣ አድርገው ሊወስዱት እንደሚችሉ መገመት አያዳግትም:: ነገር ግን እንደው አገሪቷ ውስጥ ሰው ከተገኘ ስለተቋማቶቹ ማንነትና ስለሰዎቻቸው በቀላሉ እየድህረ ገጾቻቸው ሄዶ ማወቅ ይችላል:: የእናቶ ሬድዋንን ለእኛ ብቻ ነው የተገለጥን የሚባለውን ዲስኩር ሳይሰማ ማለት ነው:: እኔም ያደረኩት ይኸው ነበረ:: በሁቱም ተቋሞች ድህረ ገጾች ላይ ድርጅቶቹ መቼና እንዴት እንደተመሰረቱ መርሆቻቸዎ ምን እንደሆኑ ምን እንደስሩና ማን ገንዘብ እንደሚለግሳቸው በግልጽ ተቀምጧል:: የቦርድ አባላቶቻቸውና መሪዋቻቸው ማን እንደሆኑ የት ይሰሩ እንደነበረ በይፋ ይታያል:: ሰዎቻቸው በመንግስትም ይሁን በግሉ ዘርፍ በጣም ውጤታማ ስራ ሰርተው የተደላደለ ኑሮ እንዳላቸው ይገመታል:: አዋን አሚሪካኖች ከግል ምቾታቸው ባላነሰ ለሰው ልጅ ደህንነት ሲባል የሚችሉትን ሲረዱ የህሌና እረፍት ያገኛሉ:: ለዚያም ነው እነዚህ ተቋማት እንደ ኢትዮጵያ ባሉት ሃገሮች የሰው ልጅ መብት ይከበር ዲሞክራሲም ይበጃችኋል እያሉ ሃባታቸውን የሚያፈሱት::የመርህ ሰዋችና ፈሪሃ እግዛብሔብር ያደረባቸው ስለሆኑና በስራቸውም የህሌና ደስታን ስለሚያገኙ ብቻ:: የለም ለእነ ሬድዋን ይህ አይደለም ምክንያቱ:: ሌላ “Corporate Interest” የሚሉት ድብቅ አላማ አለ:: አቶ ሬድዋን ይህ ድብቅ አላማ ምን ሊሆን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል:: እንድ እሳቸው ከሆነ እነዚህ ድርጅቶች ጠንክረው የሚንቀሳቀሱት በማዕድን ሃብት በተንበሸበሹ ሀገሮች ላይ ነው:: መዕልክቱ ልክ እንደ ድሮው ዘመን የደሃ አገሮችን ሃብት ሊዘርፉ ነው የሚል ይመስላል:: ጉድ በሉ አንባብዮች:: አቶ ሬድዋን አክለውም ተቋማቱ የኢትዮጵያን የመንግስት ባንኮችንና ቴሌን ወደ ግል ይዞታ ቀይሩ ብለው የሚወተውቱት እራሳቸው ሊግዙት ስለ አሰቡት ነው ብለው ያምናሉ። እንደዛማ ካልሆነ ሪፎርም አድርጉ እያሉ መጨቅጨቅ፣የዞን ዘጠኝ አባላትን ማሰልጠንን ምን አመጣው ብለው ይጠይቃሉ::
http://netsanetlegna.blogspot.de/2014/06/corporal-interest.html

No comments:

Post a Comment