Monday, June 16, 2014

ኧረ አማራዎችን ጎዳን ሲባል አማራን አጠፋን ሲባል ኢትዮጵያችንንም አጠፋናት፡፡ የአማራ ክልል ህዝብ እና መንግስት እዚህ ጉዳይ ላይ ዝምታቸው ምንድን ነው



ወለጋ አካባቢ የሚገኙ በተለይ ደግሞ ሙጊ ወረዳ የሚኖሩ አማራዎች ችግር ውስጥ ናቸው፡፡ ከፍተኛ የሆነ የመደብደብና የመሞት አደጋ በየቤታቸው ተጋርጦባቸዋል፡፡ የአካባቢው ተወላጅ ኦሮሞዎችና ከሌሎች አካባቢ የመጡ ኦሮሞዎች አማራዎችን በማሳደድና በመደብደብ ላይ ይገኛሉ፡፡
የአማራ ህዝብም ለኦሮሚያ ክልል ለአማራ ክልል እንዲሁም ለፌደራል መንግስቱ እነዚህ ዜጎች እውን ከህገ መንግስቱ ውጭ ሲንቀሳቀሱ ተገኙን እውን አሸባሪ ተብለው ነውን እውን መንግስት ይህ በአማራዎች ላይ ሲጀመር ያሴረውን ተግባሩን እስካሁን በግልፅና በገሃድ እያስኬደው ነውን
ኧረ አማራዎችን ጎዳን ሲባል አማራን አጠፋን ሲባል ኢትዮጵያችንንም አጠፋናት፡፡ የአማራ ክልል ህዝብ እና መንግስት እዚህ ጉዳይ ላይ ዝምታቸው ምንድን ነው
ይህ ሲባል የአማራ ህዝብ ለብቀላ መዘጋጀቱ ስህተት ነው ነገር ግን ቢያንስ እነዚህ ዜጎች የትኛወውም የኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ተንቀሳቅሶ የመስራት ሃብት የማፍራት መብት አላቸው፡፡ ህገመንግስቱ መብት ሰጧቸዋል፡፡ አማራ በመሆናቸው ብቻ እየታደኑ እንደ ዱር አውሬ እየተገደሉ እየታረዱ ናቸው፡፡ እውነት አቤት የመሚልላቸው ዘመድ የላቸውም ወይ፡፡ ዛር ማለትም በ28/08/2006 በሙጊ ወረዳ ያሉ አማራዎች ሲደበደቡ ውለዋል የሞቱም እንዳሉ ንብረታቸው የጋየባቸው እንዳሉም ምንጮቻችን እየተናገሩ ሲሆን እስከቀኑ 9፡00 ድረስ ምንም አይነት ጩኸታቸውን ሰምቶ የደረሰላቸው የኦሮሚያ ልዩ ሃይልም ይሑን ፖሊስ እንዲሁም ፌደራል ፖሊስ የለም፡፡
ኧረ ምንድን ነው እየሆነ ያለው
አማራ ኢትዮጵያዊ አደለም ወይ
አማራ ለኢትዮጵያ አንድነት እና ህልውና አጥኝቱን አልከሰከሰም ደሙንስ አላፈሰሰም
አሁንም ይህንን ጉዳይ ሁላችንም ሸር በማድረግ የወገኖቻችን ኢትዮጵያዊያንንን ህይወት ማዳንና ስህተት የሰራውን አካልም እርምት እንዲወስድ ማድረግ ግፊት ማድረግ አለብን፡፡ ለሃይል መልሱ ሃይል ይሁን ግን የሚል ምክር የለንም፡፡ የአማራ ህዝብ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ የአማራ ህዝብ ኢትዮጵያ ውስጥ ልክ እንደሌሎቹ ብሄር አባላት ሁሉ የትም ቦታ ተንቀሳቅሶ ክልል ቀበሌ ወረዳ ዞን ምናምን ሳይገድበው የመስራት መብት አለው፡፡
ይህን መብቱ እንዲነፈግና የስልጣኝ እድሜ ዘመኑ እንዲራዘም ሲል ይህ ደደብ ስርዓት ከሚፈነቅላቸው ድንጋዮች እና ስትራቴጅዎች መካከል አማራውን ህዝብ በክለሉ ብቻ እንዲወሰን ማድረግና ደክሞ ግሮ ጥሮ ያፈራወውን ንብረት ማውደምና ጥንካሬና በራስ መተማመኑን ማላሸቅ ነው ስለዚህ ሁላችንም ይህ የኢህአዴግና ደጋፊዎቹ አማራውና ኦሮሞው አንድ እንዳይሆን የሚጥሩ አካላት ሴራ መሆኑን አውቀን ከመጥፎ ተግባራችን መታቀብ አለብን፡፡
ለተከበረውና ለተወደደው ውድ የኦሮሞኛ ቋንቋ ተናጋሪ ህዝቦች ሆይ ይህ ነንሰንስ መንግስት ሳናደርገው መንግስት ነኝ የሚለን ገዣችን ሳናደርገው ገዥ የሆነብን ርካሽ ስርዓት የስልጣን እድሜውን ለማራዘም እንደ መስዋዕትነት ያቀረበው የአማራውና የኦሮሞው ህዝብን ማባላትና ማስተራረድ ነውና እንደ ስትራቴጅ የያዘው ከአሁኑ ነቅታችሁበት አማራውን በማሳደድ ጊዜያችን የነፃነት ትግላችን ወደኋላ በማጓተት ስራ ላይ መጠመዳችን ማቆም አለብን፡፡
አማራው ለኦሮሞው አንድ ደም ነው ኦሮሞው ለአማራው እዲሁም ለሌሎች አንድ ደም ነው አንድ ዘር ነው፡፡ ሁላችንም ኢትዮጵያዊያን አንድ ለአንድ ነን፡፡ በምንም መልኩ በመሃላችን ያለውን ክፍተት አስፍተን ራሳችን የማያልቀውን ለመጨራረስ አንሞክር፡፡ አማራ ክልል ላይ የሚኖሩ ትግራይ ውስጥ የሚኖሩ ሶማሌ ውስጥ ደቡብ ውስጥ አፋር ውስጥ የሚኖሩ በርካታ ሚሊዮን ኦሮሞዎች ሁሉ በሰላም ሰርተው እየገቡ እየኖሩ ነው፡፡ እንርሱ ያሉት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡ ኦሮምኛ ተናጋሪ ህዝብ መሃል ውስጥ የሚኖር አማርኛ ተናጋሪም ይሑን ትግረኛ ተናጋሪ ሁሉ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያሉት፡፡
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ናቸው፡፡ የትኛውም ኢትዮጵያዊ ቢፈልግ ጎንደር ቢፈልግ ናዝሬት ወለጋ ቢፈልግ ሐዋሳ ቢፈልግ አርባ ምንጭ ቢፈልግ ጅግጅጋ ቢፈልግ ሰመራ ቢፈልግ መቀሌ የትም ቢፈልግ አሶሳ የፈለገው የኢትዮጵያ ምድር ሁሉ የመኖር መብት አለው ማንም ሊያግደው አይገባም፡፡ ይህ መብቱ የተከበረ እንዲሆን ደግሞ የትኛው ክልል ማለትም የሰፈረበት አካባቢ አስተዳዳሪ ክልልም ሆነ የመጣበት ክልል ይህንን መብቱን ሊገሱበት ሊከለክሉት አይገባም፡፡
የአማራ ክልል የኦሮሚያ ክልል መንግስታትና የፌደራል ምንግስት ለዚህ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጠን እንፈልጋለን
አለበለዚያ ግን ሁላችንም የትኛውም ኢትዮጵያ ክልል የምንኖር የሁሉም ብሄር ተወላጅ ኢትዮጵያዊያን ለወገኖቻችን መብት ነገም ከዛም በኋለም ለሁላችንም መብት መከበር አደባባይ ወጥተን መታገልና መጮህ አለብን፡፡
ተቃዋሚ ፓርቲዎችም በዚህ ጉዳይ ላይ አጣርታችሁ የራሳችሁን እርምጃ መፍትሄ እንድትወስዱ በኢትዮጵያዊው ስም እንጠይቃለን፡፡ ይህ አማራዎችን ብቻ ሳይሆን የትኛውንም ኢትዮጵያዊ ወደ ክልልህ ግባ ብሎ ማፈናቀል የማሳደድ ተገባር ላይ መሳተፍ  የኦሮሞን ህዝብ የሚወክሉ ሳይሆኑ የመንግስትን ሴራ እና የቆየ ተንኮል አራማጆች ትንኮሳ እንደሆነ እኛ ኢትዮጵያዊያኝን ጠንቅቀን የምናው በመሆኑ ከዚህ ሴራችሁ ታቀቡ እንላለን፡፡
ይህን ለማውገዝ የትኛውን ኢትዮጵያዊ አማራ ኦሮሞ ትግሬ አፋር ሶማሌ ጉሙዝ ጋምቤላ ደቡብ ማንም ሳይል ሁላችንም ባገኘነው የመቃወሚያ መንገድና አጋጣሚ ሁሉ መጮኽ መከላከል አለብን፡፡
እስቲ ኢትዮጵያ ውስጥ ያልሆነ ማን ነው
አማራ ክልል ውስጥ ስንት ሚሊዮኝ ኦሮሞዎች እንዳሉ ለምን ማወቅ ተሳናችሁ ትግራይ ውስጥ ስንት ሚሊዮን ኦሮሞች አሉ አስቡት ሶማሌ ውስጥ አዲስ አበባ ውስጥ አፋር ውስጥ የትኛውም ክል ውስጥ ስንት እና ስንት ሚሊዮን ኦሮሞዎች እንደሚኖሩ ጠንቅቆ ማወቅ ያሻል፡፡ ስለዚህ የትም ያለን ኢትዮጵያዊያንና የሃገራችን ወዳጆች ሁሉ ይህን ማፈናቀል እና ማሳደድ መግደል መዝረፍ ተግባር እጅግ አምርረን ልናወግዝ ይገባል፡፡
መንግስትና ሌሎች እጃችሁን የማፈናቀሉ ሴራ ውስጥያስገባችሁ አካላት ይህን በደም የተነከረ ርካሽና ቆሻሻ እጃችሁን ከየትኛውም ኢትዮጵያዊ ላይ አንሱ፡፡ ይህንን ተግባርም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ማውገዝ አለበት ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ሌሎች የሚመለከታቸው ድርጅቶችም የአቋም መግለጫ ማውጣት አለባቸው፡፡
ኢትዮጵያዊ ነን ኢትዮጵያዊ ነው ኢትዮጵያዊ ናቸው!!!!!

No comments:

Post a Comment